Thursday 27 June 2013

ሚካኤል (ወልቃይቴ) ብሩ እና ዳውቲ-ዋይሊ

ሚካኤል (ወልቃይቴ) ብሩ እና ዳውቲ-ዋይሊ
የብሪታኒያው ዋና መላክተኛና ባልደረባዎቹ አዲስ አበባ ላይ የተደበደቡ ዕለት።

ዚህ ትረካ ደራሲ ከዚህ በፊት “የየዋሖቹ ዘመን” ባልኩት ጽሑፌ መተዋወቃችንን ለማስትወስ ያህል፤ በዕምዬ ምኒልክ ዘመን በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ በቅሎው እሰው ማሳ ውስጥ ይገባና የአቅሙን ያህል የጤፍ እሸት አጋበሶ ከዋጠ በኋላ የተፈጥሮው ግዳጅ ቢሆንበት፣ በቀረው ሰብል ላይ እየተንከባለለ መዥገር ማላቀቂያ አድርጎ ያወድመዋል። ኦሮምኛ ተናጋሪው የማሳው ባለቤት  ታዲያ የካሣውን አሞሌ ጨው ቢጠይቅ የቋንቋ አለመግባባት ሆነና፤ ከማሳው ጠቅላላ ምርት ግምት በላይ ከአንድ ብር ሁለት ብር፤ ሦስት ብር፣ አራት ብር ቢከፈለው  ጊዜ በቅሎውን እንደልቡ እንዲሰድበት መነገሩን ያጫወተን ሻለቃ ሄንሪ ዳርሊ መሆኑን ከወዲሁ አንባቢ ይገንዘብልኝ!

Monday 24 June 2013

የኢትዮጵያ የአበባ ምርት በአፍጋኒስታን ገበያ አገኘ እንዴ ?

ይመኩ ታምራት (ከሎንዶን)

ሰኞ ሰኔ 17 ቀን 2005 ዓ/ም

ሐቅ! የአየር መንገዳችን የጭነት ጥያራዎች በግንቦት እና በያዝነው ሰኔ ወራት ወደ አፍጋኒስታን ደፋ ቀና ሲሉ ታይተዋል። (Flight Radar24.com ድረ-ገጽን ይመልከቱ)

ሐቅ! አየር መንገዱ ስድስት የጭነት ጥያራዎችን አሰማርቶ በቋሚ መልክ ወደ አውሮፓ፤ መካከለኛው ምሥራቅ እና እስያ ሸቀጣ
ሸቀጥ ያመላልሳል። ኾኖም አፍጋኒስታን በቋሚነት ከሚበርባቸው አገሮች መኻል ያልተመዘገበች ከመሆኗም ባሻገር በጦርነት ከተዘፈቀች አገር ጋር ምን ዓይነት ንግድ ተጀመሮ ይሆን የሚያስብሉ ሰባት በረራዎች ቀልቤን ሊስቡት ችለዋል።

ሐቅ!  አፍጋኖቹ ያለፉትን ሦስት-አሥርት ያህል ዓመታት ያሳለፉት እርስ በርስ በመፋጀት፤ በመፈራረቅ አገራቸውን የያዙባቸውን የሁለቱን ኃያላን መንግሥታት ወራሪ ሠራዊቶች በመከላከል እና በመኻሉም አክራሪ-ሃይማኖተኝነትን መርኅ በማድረግ ነው። የአገራቸው መልክዓ-ምድር እንደ ኢትዮጵያ ተራራማ ከመኾኑም ባሻገር የገጠሩ ዜጋ አኗኗር የኛውኑ ገጠሬ ጋር ይመሳሰላል። በጎቻቸው እንኳ በላት ምትክ ቂጣሞች ይሁኑ እንጂ የኛውኑ የአዳል ሙክት ነው የሚመስሉት።  ግን ከኋላቸው ሲያስጠ................ሉ!!

Wednesday 19 June 2013

የቡድን ስምንት ወጥ ቀማሽ

«የቡድን ስምንት መሪዎች መለስ ዜናዊን የሚተካ ወጥ ቀማሽ እያፈላለጉ ነው» ተባለ።

ይመኩ ታምራት

ከአዲስ አበባ ዕሮብ ሰኔ ፭ ቀን ፳፻፭ ዓ/ም ተነስተው ቻይና ከመግባታቸው በፊት ለጢያራቸውም  ለተከታዮቻቸውም እህል ውሀ ለማለት ሳይሆን አይቀርም፤ የባንግላዴሽ ዋና ከተማ ከሚገኘው ‘ሀዝራት ሻሃጃላል ጢያራ ጣቢያ’ አረፍ ብለው ነበር። በማግሥቱ የቻይናው ጠቅላይ ሚኒስትር ሊ ኬቂያንግ ጥያራ ጣቢያ ተገኝተው ተቀበሏቸው። ዓርብ ደግሞ ከአዲሱ የቻይና ፕሬዚደንት ጋር ውይይት አደረጉ። ቅዳሜን እዚያው ውለው አድረው እሑድ ከአገር ወደተነሱበት ቁም ነገር ለመመለስ ወደሎንዶን ‘ስታንስተድ’ ጥይራ ጣቢያ አመሩ። የሎንዶኑ አቀባበል ከቤይጂንጉ የላቀ ይሁን የደበዘዘ የምናውቀው መረጃ የለንም።

Sunday 14 April 2013

“ተፈራ ደገፌ በቫንኩቨር ፀጉር ማስተካከያ ቤት የዘረኝነት መድሎ ተፈጸመብኝ አለ”


ኼንን ዘገባ ይዞ የቀረበው ጋዜጣ “የዕለቱ ዩቢሲ” (The Daily Ubyssey) የሚባለው የ’ብሪቲሽ ኮለምቢያ ዩኒቨርሲቲ’ ልሣን ሲሆን ታሪኩን ያዘለው ዕትም ለንባብ የቀረበው ዓርብ መስከረም ፲፭ ቀን /ም ነበር።  ልክ ነዎት አልተሳሳቱም! አሥራ ዘጠኝ መቶ አርባ ዓመተ ምሕረት፤ የዛሬ ስድሳ ስድስት ዓመት ማለት ነው!

Sunday 3 February 2013

አስፋ ወሰን ኃይለ ሥላሴ - ክፍል ፪


«እሳት በሌለበት ጭስ የለም!» ወይስ «ላም ባልዋለበት ኩበት ለቀማ!» ?


ክፍል ላይ በልዑል አልጋ ወራሽ መርዕድ አዝማች አስፋ ወሰን ኃይለ ሥላሴ ስም ተጻፈ የተባለ፤ ሕሊናን የሚረብሹ ነጥቦችን ያዘለ ደብዳቤ ተመልክተናል። በታኅሣሥ ፶፫ቱም የመፈንቅለ መንግሥት ሙከራ ያተረፉትን፤ እንደሙጫ ስማቸው ላይ ተጣብቆ የቀረውን ሐሜታም ተመልክተናል።

፪ኛው ክፍል ደግሞ የምንዳስሳቸው የብሪታኒያ ብሔራዊ ቤተ መዛግብት ሰነዶች በተለያዩ ጊዜያት አልጋ ወራሹ ከብሪታኒያ ርዕሰ-ልዑካን እና ከአሜሪካው ርዕሰ-ልዑካን ጋር ያካሄዷቸውን ሰፊ ውይይቶችና በወቅቱ የአገር ፖለቲካ ላይ ለነኚሁ የባዕድ መንግሥታት ወኪሎች የሰጡትን አስተያየት ያካትታል።

Sunday 27 January 2013

አስፋ ወሰን ኃይለ ሥላሴ - ክፍል ፩


(ከድል እስከ ታኅሣሡ ጉሽ)

ቻርድ ግሪንፊልድ የልዑል አልጋ ወራሽ መርዕድ አዝማች አስፋ ወሰን ኃይለ ሥላሴን ሞት ተከትሎ በብሪታንያው ‘ኢንዲፔንደንት’ ጋዜጣ ላይ በጻፉት የሙት መወድስ (ኦቢችዋሪ) ላይ «መስከረም ፲፯ ቀን ፲፱፻፱ / መኳንንቱ እና  የቤተ ክርስቲያን ሊቃውንቱ በተሰበሰቡበት አቡነ ማቴዎስ የልጅ ኢያሱን መሻር እና መወገዝ ሲያበስሩ፤ ሕፃኑ አስፋ ወሰን በአንቀልባ ታዝሎ ከሁለት አሽከሮች ጋር እንግሊዝ ለጋሲዮን ተደብቆ ነበር።»[1] ይላሉ።

Monday 21 January 2013

ወይዘሮ ዘውዲቱ፤ ራስ ጉግሳ ወሌ እና ቀብራራው አርምብራስተር!



ንደው እመ-ብርሃንን ወገኖቼ፤ የነጮች ጥጋብ ሁሌ እንደገረመኝ ነው!

እውነት ነው በአሥራ ዘጠነኛው እና በከፊልም ቢሆን በሀያኛው መቶ ክፍለ ዘመን፤ በተለይም እንግሊዞቹ እና ፈረንሳይቹ ጉልበተኛ ፈላጭ ቆራጭ ስለነበሩ የንቀታችውን መጠን ግፋ ቢል፤ በአዕምሮ ሚዛን ልንረዳላቸው እንችል ይሆናል። ያውም እኛ ኢትዮጵያውያን እራሳችንን ከሌሎቹ ገለል አድርገን የነጮቹን አስተሳሰብ የተገነዝብልናቸው እንደሆነ ነው።
ወደዋናው ጉዳይ ከመመለሴ በፊት አንድ የሰማሁትን ላካፍላችሁ።  በሃያኛው መቶ ክፍለ-ዘመን አገር ለመጎብኘት (መጎብኘት ሲባል መሰለል ብለው ያንብቡ!!!!) የገባ እንግሊዛዊ ወደአገሩ ለመመለስ በባቡር ከአዲስ አበባ ወደ ጂቡቲ እያመራ ነው።  እንግሊዛዊው እንደለመደው በአንደኛ ደረጃ ክፍል እያነጎደ ነው። የእኛ ሰዎች ግን በገዛ አገራቸው፤ የአንደኛ ደረጃውን ካርኔ ከአቅም በላይ እንዲሆን አድርገውባቸው ይሆናል፤ ብቻ ምን አደከማችሁ አንባብያን! በሦስተኛ ማዕርግ ላይ ነው ከመቶ ወደ ዘጠና ዘጠኝ ነጥብ ስድስት የሚያክሉት ተሣፋሪዎች የተጨቀጨቁት። (ነጥብ ስድስቱ ታዳጊ ወጣት መሆኑ ይሆን? ለነገሩ ግን ይሄ  ዘጠና ዘጠኝ ነጥብ ስድስት የሚሉ አመዛዘን ያኔም ነበር ማለት ነው? ወይስ አዲስነቱ ለሕዝብ ሸንጎ ቆጠራ ነው? )