«እሳት በሌለበት ጭስ የለም!» ወይስ «ላም ባልዋለበት ኩበት ለቀማ!» ?
በክፍል
፩ ላይ በልዑል አልጋ ወራሽ መርዕድ አዝማች አስፋ ወሰን ኃይለ ሥላሴ ስም ተጻፈ የተባለ፤ ሕሊናን የሚረብሹ ነጥቦችን ያዘለ ደብዳቤ ተመልክተናል። በታኅሣሥ ፶፫ቱም የመፈንቅለ መንግሥት ሙከራ ያተረፉትን፤ እንደሙጫ ስማቸው ላይ ተጣብቆ የቀረውን ሐሜታም ተመልክተናል።
በ ፪ኛው ክፍል
ደግሞ የምንዳስሳቸው የብሪታኒያ ብሔራዊ ቤተ መዛግብት ሰነዶች በተለያዩ ጊዜያት አልጋ ወራሹ ከብሪታኒያ ርዕሰ-ልዑካን እና ከአሜሪካው ርዕሰ-ልዑካን ጋር ያካሄዷቸውን ሰፊ ውይይቶችና በወቅቱ የአገር ፖለቲካ ላይ ለነኚሁ የባዕድ መንግሥታት ወኪሎች የሰጡትን አስተያየት ያካትታል።