Showing posts with label Crown Prince Asfawossen. Show all posts
Showing posts with label Crown Prince Asfawossen. Show all posts

Sunday 3 February 2013

አስፋ ወሰን ኃይለ ሥላሴ - ክፍል ፪


«እሳት በሌለበት ጭስ የለም!» ወይስ «ላም ባልዋለበት ኩበት ለቀማ!» ?


ክፍል ላይ በልዑል አልጋ ወራሽ መርዕድ አዝማች አስፋ ወሰን ኃይለ ሥላሴ ስም ተጻፈ የተባለ፤ ሕሊናን የሚረብሹ ነጥቦችን ያዘለ ደብዳቤ ተመልክተናል። በታኅሣሥ ፶፫ቱም የመፈንቅለ መንግሥት ሙከራ ያተረፉትን፤ እንደሙጫ ስማቸው ላይ ተጣብቆ የቀረውን ሐሜታም ተመልክተናል።

፪ኛው ክፍል ደግሞ የምንዳስሳቸው የብሪታኒያ ብሔራዊ ቤተ መዛግብት ሰነዶች በተለያዩ ጊዜያት አልጋ ወራሹ ከብሪታኒያ ርዕሰ-ልዑካን እና ከአሜሪካው ርዕሰ-ልዑካን ጋር ያካሄዷቸውን ሰፊ ውይይቶችና በወቅቱ የአገር ፖለቲካ ላይ ለነኚሁ የባዕድ መንግሥታት ወኪሎች የሰጡትን አስተያየት ያካትታል።

Sunday 27 January 2013

አስፋ ወሰን ኃይለ ሥላሴ - ክፍል ፩


(ከድል እስከ ታኅሣሡ ጉሽ)

ቻርድ ግሪንፊልድ የልዑል አልጋ ወራሽ መርዕድ አዝማች አስፋ ወሰን ኃይለ ሥላሴን ሞት ተከትሎ በብሪታንያው ‘ኢንዲፔንደንት’ ጋዜጣ ላይ በጻፉት የሙት መወድስ (ኦቢችዋሪ) ላይ «መስከረም ፲፯ ቀን ፲፱፻፱ / መኳንንቱ እና  የቤተ ክርስቲያን ሊቃውንቱ በተሰበሰቡበት አቡነ ማቴዎስ የልጅ ኢያሱን መሻር እና መወገዝ ሲያበስሩ፤ ሕፃኑ አስፋ ወሰን በአንቀልባ ታዝሎ ከሁለት አሽከሮች ጋር እንግሊዝ ለጋሲዮን ተደብቆ ነበር።»[1] ይላሉ።