Showing posts with label የታሪክ አውሎ ነፋስ. Show all posts
Showing posts with label የታሪክ አውሎ ነፋስ. Show all posts

Thursday 27 June 2013

ሚካኤል (ወልቃይቴ) ብሩ እና ዳውቲ-ዋይሊ

ሚካኤል (ወልቃይቴ) ብሩ እና ዳውቲ-ዋይሊ
የብሪታኒያው ዋና መላክተኛና ባልደረባዎቹ አዲስ አበባ ላይ የተደበደቡ ዕለት።

ዚህ ትረካ ደራሲ ከዚህ በፊት “የየዋሖቹ ዘመን” ባልኩት ጽሑፌ መተዋወቃችንን ለማስትወስ ያህል፤ በዕምዬ ምኒልክ ዘመን በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ በቅሎው እሰው ማሳ ውስጥ ይገባና የአቅሙን ያህል የጤፍ እሸት አጋበሶ ከዋጠ በኋላ የተፈጥሮው ግዳጅ ቢሆንበት፣ በቀረው ሰብል ላይ እየተንከባለለ መዥገር ማላቀቂያ አድርጎ ያወድመዋል። ኦሮምኛ ተናጋሪው የማሳው ባለቤት  ታዲያ የካሣውን አሞሌ ጨው ቢጠይቅ የቋንቋ አለመግባባት ሆነና፤ ከማሳው ጠቅላላ ምርት ግምት በላይ ከአንድ ብር ሁለት ብር፤ ሦስት ብር፣ አራት ብር ቢከፈለው  ጊዜ በቅሎውን እንደልቡ እንዲሰድበት መነገሩን ያጫወተን ሻለቃ ሄንሪ ዳርሊ መሆኑን ከወዲሁ አንባቢ ይገንዘብልኝ!

Monday 24 June 2013

የኢትዮጵያ የአበባ ምርት በአፍጋኒስታን ገበያ አገኘ እንዴ ?

ይመኩ ታምራት (ከሎንዶን)

ሰኞ ሰኔ 17 ቀን 2005 ዓ/ም

ሐቅ! የአየር መንገዳችን የጭነት ጥያራዎች በግንቦት እና በያዝነው ሰኔ ወራት ወደ አፍጋኒስታን ደፋ ቀና ሲሉ ታይተዋል። (Flight Radar24.com ድረ-ገጽን ይመልከቱ)

ሐቅ! አየር መንገዱ ስድስት የጭነት ጥያራዎችን አሰማርቶ በቋሚ መልክ ወደ አውሮፓ፤ መካከለኛው ምሥራቅ እና እስያ ሸቀጣ
ሸቀጥ ያመላልሳል። ኾኖም አፍጋኒስታን በቋሚነት ከሚበርባቸው አገሮች መኻል ያልተመዘገበች ከመሆኗም ባሻገር በጦርነት ከተዘፈቀች አገር ጋር ምን ዓይነት ንግድ ተጀመሮ ይሆን የሚያስብሉ ሰባት በረራዎች ቀልቤን ሊስቡት ችለዋል።

ሐቅ!  አፍጋኖቹ ያለፉትን ሦስት-አሥርት ያህል ዓመታት ያሳለፉት እርስ በርስ በመፋጀት፤ በመፈራረቅ አገራቸውን የያዙባቸውን የሁለቱን ኃያላን መንግሥታት ወራሪ ሠራዊቶች በመከላከል እና በመኻሉም አክራሪ-ሃይማኖተኝነትን መርኅ በማድረግ ነው። የአገራቸው መልክዓ-ምድር እንደ ኢትዮጵያ ተራራማ ከመኾኑም ባሻገር የገጠሩ ዜጋ አኗኗር የኛውኑ ገጠሬ ጋር ይመሳሰላል። በጎቻቸው እንኳ በላት ምትክ ቂጣሞች ይሁኑ እንጂ የኛውኑ የአዳል ሙክት ነው የሚመስሉት።  ግን ከኋላቸው ሲያስጠ................ሉ!!

Wednesday 19 June 2013

የቡድን ስምንት ወጥ ቀማሽ

«የቡድን ስምንት መሪዎች መለስ ዜናዊን የሚተካ ወጥ ቀማሽ እያፈላለጉ ነው» ተባለ።

ይመኩ ታምራት

ከአዲስ አበባ ዕሮብ ሰኔ ፭ ቀን ፳፻፭ ዓ/ም ተነስተው ቻይና ከመግባታቸው በፊት ለጢያራቸውም  ለተከታዮቻቸውም እህል ውሀ ለማለት ሳይሆን አይቀርም፤ የባንግላዴሽ ዋና ከተማ ከሚገኘው ‘ሀዝራት ሻሃጃላል ጢያራ ጣቢያ’ አረፍ ብለው ነበር። በማግሥቱ የቻይናው ጠቅላይ ሚኒስትር ሊ ኬቂያንግ ጥያራ ጣቢያ ተገኝተው ተቀበሏቸው። ዓርብ ደግሞ ከአዲሱ የቻይና ፕሬዚደንት ጋር ውይይት አደረጉ። ቅዳሜን እዚያው ውለው አድረው እሑድ ከአገር ወደተነሱበት ቁም ነገር ለመመለስ ወደሎንዶን ‘ስታንስተድ’ ጥይራ ጣቢያ አመሩ። የሎንዶኑ አቀባበል ከቤይጂንጉ የላቀ ይሁን የደበዘዘ የምናውቀው መረጃ የለንም።

Sunday 14 April 2013

“ተፈራ ደገፌ በቫንኩቨር ፀጉር ማስተካከያ ቤት የዘረኝነት መድሎ ተፈጸመብኝ አለ”


ኼንን ዘገባ ይዞ የቀረበው ጋዜጣ “የዕለቱ ዩቢሲ” (The Daily Ubyssey) የሚባለው የ’ብሪቲሽ ኮለምቢያ ዩኒቨርሲቲ’ ልሣን ሲሆን ታሪኩን ያዘለው ዕትም ለንባብ የቀረበው ዓርብ መስከረም ፲፭ ቀን /ም ነበር።  ልክ ነዎት አልተሳሳቱም! አሥራ ዘጠኝ መቶ አርባ ዓመተ ምሕረት፤ የዛሬ ስድሳ ስድስት ዓመት ማለት ነው!

Sunday 3 February 2013

አስፋ ወሰን ኃይለ ሥላሴ - ክፍል ፪


«እሳት በሌለበት ጭስ የለም!» ወይስ «ላም ባልዋለበት ኩበት ለቀማ!» ?


ክፍል ላይ በልዑል አልጋ ወራሽ መርዕድ አዝማች አስፋ ወሰን ኃይለ ሥላሴ ስም ተጻፈ የተባለ፤ ሕሊናን የሚረብሹ ነጥቦችን ያዘለ ደብዳቤ ተመልክተናል። በታኅሣሥ ፶፫ቱም የመፈንቅለ መንግሥት ሙከራ ያተረፉትን፤ እንደሙጫ ስማቸው ላይ ተጣብቆ የቀረውን ሐሜታም ተመልክተናል።

፪ኛው ክፍል ደግሞ የምንዳስሳቸው የብሪታኒያ ብሔራዊ ቤተ መዛግብት ሰነዶች በተለያዩ ጊዜያት አልጋ ወራሹ ከብሪታኒያ ርዕሰ-ልዑካን እና ከአሜሪካው ርዕሰ-ልዑካን ጋር ያካሄዷቸውን ሰፊ ውይይቶችና በወቅቱ የአገር ፖለቲካ ላይ ለነኚሁ የባዕድ መንግሥታት ወኪሎች የሰጡትን አስተያየት ያካትታል።