Showing posts with label የኢትዮጵያ አየር መንገድ. Show all posts
Showing posts with label የኢትዮጵያ አየር መንገድ. Show all posts

Monday 24 June 2013

የኢትዮጵያ የአበባ ምርት በአፍጋኒስታን ገበያ አገኘ እንዴ ?

ይመኩ ታምራት (ከሎንዶን)

ሰኞ ሰኔ 17 ቀን 2005 ዓ/ም

ሐቅ! የአየር መንገዳችን የጭነት ጥያራዎች በግንቦት እና በያዝነው ሰኔ ወራት ወደ አፍጋኒስታን ደፋ ቀና ሲሉ ታይተዋል። (Flight Radar24.com ድረ-ገጽን ይመልከቱ)

ሐቅ! አየር መንገዱ ስድስት የጭነት ጥያራዎችን አሰማርቶ በቋሚ መልክ ወደ አውሮፓ፤ መካከለኛው ምሥራቅ እና እስያ ሸቀጣ
ሸቀጥ ያመላልሳል። ኾኖም አፍጋኒስታን በቋሚነት ከሚበርባቸው አገሮች መኻል ያልተመዘገበች ከመሆኗም ባሻገር በጦርነት ከተዘፈቀች አገር ጋር ምን ዓይነት ንግድ ተጀመሮ ይሆን የሚያስብሉ ሰባት በረራዎች ቀልቤን ሊስቡት ችለዋል።

ሐቅ!  አፍጋኖቹ ያለፉትን ሦስት-አሥርት ያህል ዓመታት ያሳለፉት እርስ በርስ በመፋጀት፤ በመፈራረቅ አገራቸውን የያዙባቸውን የሁለቱን ኃያላን መንግሥታት ወራሪ ሠራዊቶች በመከላከል እና በመኻሉም አክራሪ-ሃይማኖተኝነትን መርኅ በማድረግ ነው። የአገራቸው መልክዓ-ምድር እንደ ኢትዮጵያ ተራራማ ከመኾኑም ባሻገር የገጠሩ ዜጋ አኗኗር የኛውኑ ገጠሬ ጋር ይመሳሰላል። በጎቻቸው እንኳ በላት ምትክ ቂጣሞች ይሁኑ እንጂ የኛውኑ የአዳል ሙክት ነው የሚመስሉት።  ግን ከኋላቸው ሲያስጠ................ሉ!!