Showing posts with label Empress Zewditu and Armbruster. Show all posts
Showing posts with label Empress Zewditu and Armbruster. Show all posts

Monday 21 January 2013

ወይዘሮ ዘውዲቱ፤ ራስ ጉግሳ ወሌ እና ቀብራራው አርምብራስተር!



ንደው እመ-ብርሃንን ወገኖቼ፤ የነጮች ጥጋብ ሁሌ እንደገረመኝ ነው!

እውነት ነው በአሥራ ዘጠነኛው እና በከፊልም ቢሆን በሀያኛው መቶ ክፍለ ዘመን፤ በተለይም እንግሊዞቹ እና ፈረንሳይቹ ጉልበተኛ ፈላጭ ቆራጭ ስለነበሩ የንቀታችውን መጠን ግፋ ቢል፤ በአዕምሮ ሚዛን ልንረዳላቸው እንችል ይሆናል። ያውም እኛ ኢትዮጵያውያን እራሳችንን ከሌሎቹ ገለል አድርገን የነጮቹን አስተሳሰብ የተገነዝብልናቸው እንደሆነ ነው።
ወደዋናው ጉዳይ ከመመለሴ በፊት አንድ የሰማሁትን ላካፍላችሁ።  በሃያኛው መቶ ክፍለ-ዘመን አገር ለመጎብኘት (መጎብኘት ሲባል መሰለል ብለው ያንብቡ!!!!) የገባ እንግሊዛዊ ወደአገሩ ለመመለስ በባቡር ከአዲስ አበባ ወደ ጂቡቲ እያመራ ነው።  እንግሊዛዊው እንደለመደው በአንደኛ ደረጃ ክፍል እያነጎደ ነው። የእኛ ሰዎች ግን በገዛ አገራቸው፤ የአንደኛ ደረጃውን ካርኔ ከአቅም በላይ እንዲሆን አድርገውባቸው ይሆናል፤ ብቻ ምን አደከማችሁ አንባብያን! በሦስተኛ ማዕርግ ላይ ነው ከመቶ ወደ ዘጠና ዘጠኝ ነጥብ ስድስት የሚያክሉት ተሣፋሪዎች የተጨቀጨቁት። (ነጥብ ስድስቱ ታዳጊ ወጣት መሆኑ ይሆን? ለነገሩ ግን ይሄ  ዘጠና ዘጠኝ ነጥብ ስድስት የሚሉ አመዛዘን ያኔም ነበር ማለት ነው? ወይስ አዲስነቱ ለሕዝብ ሸንጎ ቆጠራ ነው? )